Telegram Group & Telegram Channel
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (18)

13. ንግግርህ ብቁ ይሁን (ሐ)

4. ስለ ማታወቀው ነገር አትናገር

“ውኃ ዋናና ትዳር በምክር አይታወቅም” ይባላል ። ገብተህ ማየት አለብህ ማለት ነው ። ስለ ትዳር ግን አብዝቶ የመከረው ከጴጥሮስ ይልቅ ድንግል ጳውሎስ ነው ። ስለማታውቀው ነገር መጻሕፍትን አገላብጥ ፣ አዋቂዎችን ጠይቅ ። ሁሉን አውቃለሁ ማለት እኔ እግዚአብሔር ነኝ ብሎ እንደ መናገር ነው ። ምንም የማናውቅ ደግሞም ሁሉን የምናውቅ ሆነን አልተፈጠርንም ። እግዚአብሔር ለማንም ጸጋን ጠቅልሎ በጅምላ አልሰጠም ። አንዱ አንዱን እንዲፈልግ እውቀትና ጸጋ ተከፋፍሎ ተሰጥቷል ። የመረጃ እውቀት ለፍላፊ ፣ የሥነ ልቡና እውቀት ብልጥ ሊያደርጉህ ይከጅላሉና ጠንቃቃ ሁን ። መለፍለፍ ከፊት እውቀት ፣ ከኋላ ተግባር የለውም ። የኳስ ተጨዋችን ደመወዝ ማወቅ እውቀት ሳይሆን የቤት ኪራይ ለሌለን ድሆች ተራ ነገር ነው ። እነ እገሌ ተዋጉ ማለት ዜና እንጂ እውቀት አይደለም ። ምናልባት በዚያ አካባቢ ጉዞ ቢኖረን ለጥንቃቄ ይረዳል ። ብዙ የማናውቃቸው ነገሮች አሉ ። አውቀናቸውም ገና የሚሻሩ እውቀቶች አሉ ። በየጊዜው ሳይንሱ ራሱን እያደሰ ፣ ከሃምሳ ዓመት በፊት የመጨረሻ ያለውን እውቀት አሁን ላይ ስህተት ነበረ እያለ ነው ። ሁሉን የሚያውቁ የሚመስላቸው ሰዎች ሊሮጡ ይችላሉ ፣ ግን የሚያጠፉት ይበዛል ። ጸጋን ለባለጸጋው መተው ጊዜን ፣ ገንዘብን ፣ ሰውን ማትረፊያ ነው ። አንተ ግን ስለሁሉም ነገር አስተያየት አትስጥ ። አላዋቂ ሲናገር የተሳሳተ መረጃ መስጠቱ ብቻ ሳይሆን ሊቃውንትን ዱዳ ያደርጋቸዋል ። ዘመኑ የጆሮ ጠገቦች ነው ፣ እኛ በራችንን እንዝጋ ይላሉ ።

5. ከተናደድህ አትናገር

ፍሬኑ የተበጠሰ መኪና በትራፊክ ምልክት አይቆምም ። የሚቆመው ተጋጭቶ ወይም ተገልብጦ ነው ። ንዴትም ፍሬኑ የተበጠሰ መኪና መሆን ነው ። ንዴት እውቀትህን ፣ ለዘመናት ያካበትከውን ስምህን ፣ ወዳጅነትህን ገደል ይዞ የሚገባ ነው ። ውስጥህ እንደ ተበሳጨ ከተሰማህ እዚያ ቦታ ላይ አትቆይ ። ወዲያው ወጥተህ 500 ሜትር ጉዞ አድርግ ። ነፋሱ ሲነካህ ፣ አዲስ ነገር ስታይ ንዴትህ እየበረደ ፣ በትክክል እያሰብህ ትመጣለህ ። በንዴት ሆነህ ከትዳር አጋርህ ጋር አትነጋገር ። ጉዞው ገና ለዕድሜ ልክ ነውና ሁሉን ተናግረህ መጨረስ አያስፈልግህም ። በሥርዓት አለመነጋገር እንጂ የማያግባባ ነገር በዓለም ላይ የለም ። ሰዎች ክፉ የሚናገሩህ ክፉ ስትናገር በአንተ ስህተት ውስጥ ለመደበቅና ፣ አንተን በጸጸት ለማሰቃየት ነው ። ለሰዎች ተንኮል ምቹ አትሁንላቸው ። ቢሆንም በውስጥህ ያለውን ቅንነት የንዴት ቃል ሊሸፍነው ይችላልና ከተናደድህ አትናገር ። ንዴት ዘመድ የሚሆነው በሰዓቱ ብቻ ነው ። ወዲያው ጸጸቱ ይጀምራል ። ከሰዎች ክፋት በላይ የሚያሳስበው አንተን ክፉ እንዳያደርጉህ ነው ።

6. ንግግር አሳማሪ አትሁን

እግዚአብሔር አፈ ቅቤውን አሮንን ሳይሆን አፈ ትቡን ሙሴን እንደመረጠ አስተውል ። ንግግር በሰው ፊት ትልቅ ያሰኝ ይሆናል ። እግዚአብሔር ግን ልብንና ተግባርን ይመዝናል ። በንግግር ቢሆን በዚህ ዘመን ሁሉም አማኝ ነው ። እንዳየነው ግን በእግዚአብሔር የሚያምን ጥቂት ነው ። የዘመኑ የኑሮ ቄንጥ እግዚአብሔር እንዳለ እያወራህ እንደሌለ አድርገህ ኑር የሚል ነው ። የሰሙት ነገር ከጆሮአቸው ወደ ልባቸው ያልወረደ ፣ ምርጥ ቃል ሲያገኙ ይህን ለስብሰባዬ እያሉ የሚጨነቁ አያሌ ናቸው ። በእሳት አለንጋ እየተገረፉ ፣ በገጣሚና በተሳዳቢ የሚዝናኑ ፣ “ልኩን ነገረልኝ” እያሉ አጉል እርካታ የሚረኩ አያሌ ናቸው ። የአገራችንን መከራ ያረዘመው በሞታችን መሳለቃችን ነው ። በሥርዓት መናገር አለብህ ። ነገር ግን ሁሉም ሕይወትህ ንግግር እንደሆነ በማሰብ ስለ ጣፋጭ አገላለጥ አትጨነቅ ። ተግባርህ ካረከሰህ መቼም ቢሆን ንግግርህ አይቀድስህም ። የምትሰማውን ጥቅስ ፣ የምትሰበከውን ስብከት ፣ ያዳመጥከውን ተረት መጀመሪያ አጣጥመው ። ከዚያ በኋላ በቦታው ተናገረው ። ቃለ እግዚአብሔር እንደ እንደ ቆርቆሮ እያጠባቸው የሚሄድ፣ የማይረሰርሱ ሰሚዎችና ተናጋሪዎች አሉ ። እንደ አፈር ቦይ ረክተው ለሌላው ቢለቁ ግን ድነው ያድኑ ነበር ። ሃይማኖተኛና የሚደልልን ሰው መለየት እስኪያቅት አንድ ሆነው እያየን ነው ። እግዚአብሔር ቃሉን ለማስታወቂያ ሠራተኛ ሳይሆን ለምስክር ሰጥቷል ።

በምዕራብ አገሮች ክርስትናው እየጠፋ ያለው በቃላት አሳማሪዎች ስህተት ነው ። ያንን ስህተት ተሸክመው ወደ አገራችን የገቡት የሚስዮናውያንና የአገር አስወራሪዎች ደቀ መዛሙርት ቃላት በማሳመር እግዚአብሔርን የሚያከብሩት ይመስላቸዋል ። አንድ የአእምሮ በሽተኛ የነበሩ ፣ ዕርቃናቸውን የሚዞሩ ሰው እንዲህ እያሉ ይናገሩ ነበር ይባላል፡- “ሰው ሁሉ አብዶ ፣ እኔ ብቻ ቀረሁ ።” ዛሬም ሁሉ ጠፍቷል ፣ እኔ ብቻ ድኛለሁ የሚሉ ፣ በእኛ በኩል ካልሆነ ጌታን አታገኙም እያሉ ቃላት የሚያሳምሩ ለዚህ ትውልድና አገር ትልቅ ዕዳ ይዘው እየመጡ ነው ። ይህ ያልገባው ያገሬ ልጅ ሥነ መለኮትን በቃላት ቁማር እየለወጠ ይነጉዳል ። ካልተመለሰ መጨረሻው እግዚአብሔር የለሽ ሁኖ ይቀራል ። ለዚህም አውሮፓና ሰሜን አሜሪካ ምስክር ናቸው ። እግዚአብሔር በእውነት እንጂ በድለላ አይገኝም ።


ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም.



tg-me.com/Nolawii/3927
Create:
Last Update:

የሕይወት ሥነ ሥርዓት (18)

13. ንግግርህ ብቁ ይሁን (ሐ)

4. ስለ ማታወቀው ነገር አትናገር

“ውኃ ዋናና ትዳር በምክር አይታወቅም” ይባላል ። ገብተህ ማየት አለብህ ማለት ነው ። ስለ ትዳር ግን አብዝቶ የመከረው ከጴጥሮስ ይልቅ ድንግል ጳውሎስ ነው ። ስለማታውቀው ነገር መጻሕፍትን አገላብጥ ፣ አዋቂዎችን ጠይቅ ። ሁሉን አውቃለሁ ማለት እኔ እግዚአብሔር ነኝ ብሎ እንደ መናገር ነው ። ምንም የማናውቅ ደግሞም ሁሉን የምናውቅ ሆነን አልተፈጠርንም ። እግዚአብሔር ለማንም ጸጋን ጠቅልሎ በጅምላ አልሰጠም ። አንዱ አንዱን እንዲፈልግ እውቀትና ጸጋ ተከፋፍሎ ተሰጥቷል ። የመረጃ እውቀት ለፍላፊ ፣ የሥነ ልቡና እውቀት ብልጥ ሊያደርጉህ ይከጅላሉና ጠንቃቃ ሁን ። መለፍለፍ ከፊት እውቀት ፣ ከኋላ ተግባር የለውም ። የኳስ ተጨዋችን ደመወዝ ማወቅ እውቀት ሳይሆን የቤት ኪራይ ለሌለን ድሆች ተራ ነገር ነው ። እነ እገሌ ተዋጉ ማለት ዜና እንጂ እውቀት አይደለም ። ምናልባት በዚያ አካባቢ ጉዞ ቢኖረን ለጥንቃቄ ይረዳል ። ብዙ የማናውቃቸው ነገሮች አሉ ። አውቀናቸውም ገና የሚሻሩ እውቀቶች አሉ ። በየጊዜው ሳይንሱ ራሱን እያደሰ ፣ ከሃምሳ ዓመት በፊት የመጨረሻ ያለውን እውቀት አሁን ላይ ስህተት ነበረ እያለ ነው ። ሁሉን የሚያውቁ የሚመስላቸው ሰዎች ሊሮጡ ይችላሉ ፣ ግን የሚያጠፉት ይበዛል ። ጸጋን ለባለጸጋው መተው ጊዜን ፣ ገንዘብን ፣ ሰውን ማትረፊያ ነው ። አንተ ግን ስለሁሉም ነገር አስተያየት አትስጥ ። አላዋቂ ሲናገር የተሳሳተ መረጃ መስጠቱ ብቻ ሳይሆን ሊቃውንትን ዱዳ ያደርጋቸዋል ። ዘመኑ የጆሮ ጠገቦች ነው ፣ እኛ በራችንን እንዝጋ ይላሉ ።

5. ከተናደድህ አትናገር

ፍሬኑ የተበጠሰ መኪና በትራፊክ ምልክት አይቆምም ። የሚቆመው ተጋጭቶ ወይም ተገልብጦ ነው ። ንዴትም ፍሬኑ የተበጠሰ መኪና መሆን ነው ። ንዴት እውቀትህን ፣ ለዘመናት ያካበትከውን ስምህን ፣ ወዳጅነትህን ገደል ይዞ የሚገባ ነው ። ውስጥህ እንደ ተበሳጨ ከተሰማህ እዚያ ቦታ ላይ አትቆይ ። ወዲያው ወጥተህ 500 ሜትር ጉዞ አድርግ ። ነፋሱ ሲነካህ ፣ አዲስ ነገር ስታይ ንዴትህ እየበረደ ፣ በትክክል እያሰብህ ትመጣለህ ። በንዴት ሆነህ ከትዳር አጋርህ ጋር አትነጋገር ። ጉዞው ገና ለዕድሜ ልክ ነውና ሁሉን ተናግረህ መጨረስ አያስፈልግህም ። በሥርዓት አለመነጋገር እንጂ የማያግባባ ነገር በዓለም ላይ የለም ። ሰዎች ክፉ የሚናገሩህ ክፉ ስትናገር በአንተ ስህተት ውስጥ ለመደበቅና ፣ አንተን በጸጸት ለማሰቃየት ነው ። ለሰዎች ተንኮል ምቹ አትሁንላቸው ። ቢሆንም በውስጥህ ያለውን ቅንነት የንዴት ቃል ሊሸፍነው ይችላልና ከተናደድህ አትናገር ። ንዴት ዘመድ የሚሆነው በሰዓቱ ብቻ ነው ። ወዲያው ጸጸቱ ይጀምራል ። ከሰዎች ክፋት በላይ የሚያሳስበው አንተን ክፉ እንዳያደርጉህ ነው ።

6. ንግግር አሳማሪ አትሁን

እግዚአብሔር አፈ ቅቤውን አሮንን ሳይሆን አፈ ትቡን ሙሴን እንደመረጠ አስተውል ። ንግግር በሰው ፊት ትልቅ ያሰኝ ይሆናል ። እግዚአብሔር ግን ልብንና ተግባርን ይመዝናል ። በንግግር ቢሆን በዚህ ዘመን ሁሉም አማኝ ነው ። እንዳየነው ግን በእግዚአብሔር የሚያምን ጥቂት ነው ። የዘመኑ የኑሮ ቄንጥ እግዚአብሔር እንዳለ እያወራህ እንደሌለ አድርገህ ኑር የሚል ነው ። የሰሙት ነገር ከጆሮአቸው ወደ ልባቸው ያልወረደ ፣ ምርጥ ቃል ሲያገኙ ይህን ለስብሰባዬ እያሉ የሚጨነቁ አያሌ ናቸው ። በእሳት አለንጋ እየተገረፉ ፣ በገጣሚና በተሳዳቢ የሚዝናኑ ፣ “ልኩን ነገረልኝ” እያሉ አጉል እርካታ የሚረኩ አያሌ ናቸው ። የአገራችንን መከራ ያረዘመው በሞታችን መሳለቃችን ነው ። በሥርዓት መናገር አለብህ ። ነገር ግን ሁሉም ሕይወትህ ንግግር እንደሆነ በማሰብ ስለ ጣፋጭ አገላለጥ አትጨነቅ ። ተግባርህ ካረከሰህ መቼም ቢሆን ንግግርህ አይቀድስህም ። የምትሰማውን ጥቅስ ፣ የምትሰበከውን ስብከት ፣ ያዳመጥከውን ተረት መጀመሪያ አጣጥመው ። ከዚያ በኋላ በቦታው ተናገረው ። ቃለ እግዚአብሔር እንደ እንደ ቆርቆሮ እያጠባቸው የሚሄድ፣ የማይረሰርሱ ሰሚዎችና ተናጋሪዎች አሉ ። እንደ አፈር ቦይ ረክተው ለሌላው ቢለቁ ግን ድነው ያድኑ ነበር ። ሃይማኖተኛና የሚደልልን ሰው መለየት እስኪያቅት አንድ ሆነው እያየን ነው ። እግዚአብሔር ቃሉን ለማስታወቂያ ሠራተኛ ሳይሆን ለምስክር ሰጥቷል ።

በምዕራብ አገሮች ክርስትናው እየጠፋ ያለው በቃላት አሳማሪዎች ስህተት ነው ። ያንን ስህተት ተሸክመው ወደ አገራችን የገቡት የሚስዮናውያንና የአገር አስወራሪዎች ደቀ መዛሙርት ቃላት በማሳመር እግዚአብሔርን የሚያከብሩት ይመስላቸዋል ። አንድ የአእምሮ በሽተኛ የነበሩ ፣ ዕርቃናቸውን የሚዞሩ ሰው እንዲህ እያሉ ይናገሩ ነበር ይባላል፡- “ሰው ሁሉ አብዶ ፣ እኔ ብቻ ቀረሁ ።” ዛሬም ሁሉ ጠፍቷል ፣ እኔ ብቻ ድኛለሁ የሚሉ ፣ በእኛ በኩል ካልሆነ ጌታን አታገኙም እያሉ ቃላት የሚያሳምሩ ለዚህ ትውልድና አገር ትልቅ ዕዳ ይዘው እየመጡ ነው ። ይህ ያልገባው ያገሬ ልጅ ሥነ መለኮትን በቃላት ቁማር እየለወጠ ይነጉዳል ። ካልተመለሰ መጨረሻው እግዚአብሔር የለሽ ሁኖ ይቀራል ። ለዚህም አውሮፓና ሰሜን አሜሪካ ምስክር ናቸው ። እግዚአብሔር በእውነት እንጂ በድለላ አይገኝም ።


ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም.

BY Nolawi ኖላዊ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/Nolawii/3927

View MORE
Open in Telegram


Nolawi ኖላዊ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

How Does Telegram Make Money?

Telegram is a free app and runs on donations. According to a blog on the telegram: We believe in fast and secure messaging that is also 100% free. Pavel Durov, who shares our vision, supplied Telegram with a generous donation, so we have quite enough money for the time being. If Telegram runs out, we will introduce non-essential paid options to support the infrastructure and finance developer salaries. But making profits will never be an end-goal for Telegram.

Nolawi ኖላዊ from hk


Telegram Nolawi ኖላዊ
FROM USA